Posts

Showing posts from May, 2022

የኢየሱስን እናት ብፅዕት ማርያምን አትሳደቡ! (2)

 ማርያምን አትሳደቡ! (2) መግቢያ  1.ስሜ ማርያምና በስሜ ማርያም ፈውስ  2.ማርያም የክርስቶስ እናት መሆኗን መቼ አወቀች !? 3.የጥበብ ሰዎችና ስግደታቸው  4.አብርሃም ወደ ከነዓን ለምን ወጣ !? 5.ሎጥን ያዳነው ማን ነው !? 6.መላእክትን የሚያዘው ማን ነው !? 7.ለክርስቶስ መቃብር ጥበቃ ለምን ተቀጠረለት !? 8.ሰዎች ሁሉ ማንን ይለምናሉ !? 9.የሐዋርያት ሹመት በማርያም ነውን !?  ማጠቃለያ  ዋቢ መጽሐፍት                      መግቢያ!  ከዚህ በፊት የቀረበውን ካነበባችሁ በኃላ እንደተጠቀማችሁ ተስፋ አደርጋለሁ ።የመጀመሪያ የጹሑፌ ዓላማ የኢየሱስን እናት እኔ (እኛ) እንደማል[ን]ሳደብ እና ማን እንደ ሚሳደብ በግልጽ ማሳየት ነበር።ይዚህኛው ዓላማ ግን የስህተት ትምህርት ዲቃላ ፍሬ ስለሚያፈራ በማሳየትም የበጉ የሆኑትን መለየት ነው ። ቃሉ እንደሚል “..፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤”— ዮሐንስ 10፥4 ፣ ስለዚህም የኢየሱስ የሆኑቱ ድምጹን ለይተው ያውቃሉ ፤ የሚከተሉትም እርሱንና እርሱን ብቻና ብቻ ነው።እረኛውን ስለሚያውቁ መጽሐፍ እንደሚል “ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና።” — ዮሐንስ 10፥5 ።ስለዚህም ወዳጆቼ አንድ ሰው ሃሰተኛ ትምህርት ፦ አስተማሪ፣ነቢይ ፣ሐዋርያ .. የሚከተል ከሆነ እረኛውን የማውቅ ፣ድምጹንም የማይለይ ፣በግም ያለሆነ  በመሆኑ ነው ማለት ነው።ባይሆንማ ቃሉ እንደሚል አይከተሉም።ይሸሹም ነበር ።  ስለዚህም እንደ አንድ ክርስቲያን ሸክም እንደሚሰማው ሰው፣በእውነት ቃል ላይ ለዘመናት የተሸቃቀጠውን በመግልጽ እና...

"ደብተራ ማን ነው?" ጸረ ደብተራ ንቅናቄ በሊቀ ጠበብት በዶክተር ዘሪሁን ሙላቱ

 "ደብተራ ማን ነው?" በዶክተር ዘሪሁን ሙላቱ #ደብተራ ማን ነው??  ክፍል አንድ   “#ደብተራ” ማለት ቃሉ  ሁለት ዓይነት ምንጭ አለው ፤ አንዱ ከግእዝ ሲሆን፤ ሁለተኛው ከግሪክኛ ነው ፤ በግሪክኛው  ምንጫችን  “ደብተራ” ማለት  “ጸሐፊ" ማለት ነው ፤  በግእዙ ቋንቋ “ደብተራ” ማለት “ድንኳን” ማለት ሲሆን በውስጡ ያሉ አገልጋዮች   ካህናተ ደብተራ ይባላሉ ፡፡ ካህናተ ደብተራ የሚለውን ስያሜ በከፊል ስም ደብተራ  ብሎ ጠርቶ ካህናተ ደብተራን ለመጥራት ነው ደብተራ የሚለው አገላለጽ የመጣው የሚሉ አሉ ፤ በዚህ ምክንያት ማኅሌታይ ሲጠራ ደብተራ ተብሎ መጠራት እንደተጀመረ ይነገራል ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተጻፈው በደብተራ ኦሪት (በድንኳን)  ውስጥ ያለው የመዘምራን የዜማ አገልግሎት የደብተራ ታሪካዊ መነሻው እንደሆነ የሚጽፉ አሉ  ፡፡  #ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ ማኅሌታውያኑን ሲጠቅስ "ደብተራ" ብሎ አይጠራቸውም ፤ መዘምር ወይም መዘምራን እያለ ይጠራቸዋል ፡፡ በመጽሐፈ ነገሥት እንደተጻፈው በንጉሥ ዳዊት ፊት በድንኳን  ውስጥ የሚያገለግሉ መዘምራን  ናቸው ፡፡ ንጉሥ ሰሎሞን ቤተ መቅደሱን አሰርቶ ከጨረሰ በኋላ ከድንኳን ወደ ቤተ መቅደስ አገልግሎቱ ሲሸጋገር የድንኳኑ የደብተራ አገልግሎት በንጉሡ ፊት  ቀጥሏል ፡፡ ሥርዐቱም በቤተ እስራኤልም በቤተ ክርስቲያንም ዛሬ ድረስ አለ ፡፡  #ሊቀ ሥልጣናት ሀብተ ማርያም ወርቅነህ (አቡነ መልከጼዴቅ)  የቤተ ክርስቲያን ማኅሌታውያን የሆኑ  መዘምራን ላይ   #ደብተራ የሚለው መጠርያ ከጊዜ በኋላ የመጣ መሆኑን ጽፈዋል ፡፡ በዚህ መሠረት ይመስ...