Posts

Showing posts from July, 2022

ራዕይ ጥናት ከም.4-22

  በዓለም ለሚከሰቱ ነገሮች ከበስተጀርባ ያለውን እውነታ ለማውቅ መጽሐፍ ቅዱስን እናጥና! እንወቀው! እንጽና !                    (ራዕይ ጥናት ከም.4-22) “ከዚያ በኋላም አየሁ፥ እነሆም በሰማይ የተከፈተ ደጅ፥ እንደ መለከትም ሆኖ ሲናገረኝ የሰማሁት ፊተኛው ድምፅ፦ ወደዚህ ውጣና ከዚህ በኋላ ሊሆን የሚያስፈልገውን ነገር አሳይሃለሁ አለ።”ራእይ 4፥1 ዮሐንስ ስለ 7ቱ አብያተክርስቲያናት በአስቸኳይ ልሆን የሚገባውን ከተመለከተ በኃላ ፣ በምዕራፍ 4 ደግሞ ሌላ ገና ልሆን የሚገባው ነገር ይመለከታል ። (ራዕይ መጽሐፍ ያለፈ ታርክ እየተረከልን አይደለም ) “ወዲያው በመንፈስ ነበርሁ፤ እነሆም፥ ዙፋን በሰማይ ቆሞአል በዙፋኑም ላይ ተቀማጭ ነበረ፤”ራእይ 4፥2 ዮሐንስ አብ በዙፋኑ ተቀምጦ እያለ ይመለከታል ፣ “በዙፋኑ ዙሪያም ሀያ አራት ዙፋኖች ነበሩ፥ በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው በራሳቸውም የወርቅ አክሊል ደፍተው ሀያ አራት ሽማግሌዎች ተቀምጠው ነበር።” ራእይ 4፥4 እነዚህ 24 ሽማግሌዎች የተባሉት በብሉይና በአድስ ክዳን ያሉቱ መላው የእግዚአብሔር ቤተሰብ ቁጥር ነው ፣ “ከዙፋኑም መብረቅና ድምፅ ነጐድጓድም ይወጣል፤ በዙፋኑም ፊት ሰባት የእሳት መብራቶች ይበሩ ነበር፥ እነርሱም ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው።”ራእይ 4፥5 ዮሐንስ ስመለከት ሰባት(በሙላት) የእግዚአብሔር መንፈስ አለበት በዙፋኑ ፊት፣ “በዙፋኑም ፊት ብርሌ የሚመስል የብርጭቆ ባሕር ነበረ። በዙፋኑም መካከል በዙፋኑም ዙሪያ፥ በፊትና በኋላ ዓይኖች የሞሉአቸው አራት እንስሶች ነበሩ።”ራእይ 4፥6 ዮሐንስ ስመለከት አራት እንስሶች (በዓለም በአራቱ አጥቃጫዎች ያሉት ፍጥረታት በሙሉ በፊቱ አሉ፣...

የሐዋርያው የዮሐንስ መልእክት ለዛሬዋ ቤተክርስቲያን

የሐዋርያው የዮሐንስ መልእክት ለዛሬዋ ቤተክርስቲያን የአንደኛው መልእክት ! ተጠንቀቁ ! ዮሐንስ መልእክቱን የጻፈበት ዓላማ ከስህተት ትምህርቶች ለመጠበቅ ነው።ፍጹም ደስታ የሚኖረው በትክክለኛ ትምህርት በተመሠረተ ነው 1፥4 በማለት ለትክክለኛ ትምህርቱም የዓይን እማኝ መሆኑንም ያበስራል 1፥1-3 ።ዝም ብሎ "ኢየሱስን አምኛለሁ" ብሉ ምን ችግር አለው !? ለምን አስፈለገ የስህተት ትምህርት መቃወም !? ብሉ መልሱ ፦  “.፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤..።”1ኛ ጢሞ 3፥15 ፣እንደሚል በእግዚአብሔር ቤት ለመኖር እግዚአብሔርን መምሰል ያስፈልጋል ። “እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ 1ኛ ጢሞ 3፥16 መምሰል የተባለው ቃል በግርኩ eusébeia የሚል ቃል ነው።እውነተኛ አምልኮ ማለት ነው።ስለዚህም የእውተኛ አምልኮ ሚስጥር ታላቅ ነው መጽሐፍ ይለናል ።እውነተኛ አምልኮ አምልኮችን ለመሆን ፦ “.፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ።”1ኛ ጢሞ 3፥16 ፣ ይህንን በትክክል ማወቅ እና መቀበል ያስፈልጋል ። ልክ እንደ ሐዋርያው ጳውሎስም ሐዋርያው ዮሐንስም ሙሉ ደስታ የሚኖረው " በትክክል እኛ በዐይናችን ያየነውን እና የተመለከትነውን ፣ከእርሱም የሰማነውን ስታምኑ ነው" በማለት ይህንን የመጀመሪያ መልእክት ጽፈውልናል። ይገርማችኋል የኢየሱስ መሆን ኢየሱስ ኢየሱስ ዘወትር ማለት አይደለም።አምልኮ ዘወትር በጉባኤ መዘመርም ማሸብሸብም አይደለም ።ምክንያቱም እውነተኛ አምልኮ በትክክለኛ እውቀት የተመሠረተ ነው።በትክክለኛ እውቀት የተመሠረተ ሽብሸባም ዝማሬም የእውነተኛ አምልኮ ክፍል ነው። ስለዚህም ከዚህ...