ነገረ ታቦት
ነገረ ታቦት መግቢያ 1.የቃሉን ትርጉም 2.እንድሰራ ማን አዘዘ?ለምን ተሰራ?መቼ አዘዘ ? 3.አሰራሩን እና ስለ አሰራሩ የእግዚአብሔር አቋም! 4.ታቦቱ አሁን የት ነው ? 5. በአድሱ ኪዳን የብሉይ ታቦት አገልግሏልን ? 6.በአድስ ኪዳን አሰራሩ እና አጠቃቀሙ የተነገረለት፣ በአድስ መልክ የሚሰራ ታቦት አለን !? 7. የጌታ እራት የምንካፈልበት እቃ "ታቦት" ነውን !? 8. በአድስ ኪዳን አሰራሩ ለየት ያለ ታቦት አለ የሚሉት ለምን የብሉይን ታቦት ይጠቅሳሉ !? 9.በሰማይ ታቦት አለን !? የተኛው ነው (የብሉይ ነው ወይንስ የአድስ ኪዳን ታቦት ) ምን ማለት ነው በራሱ !? 10.የመጽሐፍ ቅዱስ ዝምታ ይከበር ! 11. ለቃሉ እና ለቃሉ ጌታ ታማኝ እንሁን ! ............................................ መግቢያ በዚህ ርዕስ ዙሪያ ለመጻፍ ያነሳሳኝ የከበረውን የእግዚአብሔርን ታቦት ነገር እንደ ቃሉ እንዲንረዳ እና እንድናውቅ ብሎም ለቃሉ ተማኝነትን ለማሳየትና ለቃሉ መሸነፍን ለማበረታታት ነው። ብዙ ግዜ ብዙ ትምህርቶች ላይ አቋም ይዤ፣ "ተሳስቻለሁ" ብዬ ፣ ከሰው ተምሬ አውቃለሁ ።ቃሉን ሳጠን ፣ ቃሉ ዘምበል ወደ ሚልበት ዘበል ማለትን ተምሬያለሁ ።ለምሳሌ የልሳን ጸጋ የለም የምል አቋም ነበረኝ ፤ትቸዋለሁ ፤ስህተትም ነበር።ይህንን በማድረጌ ተጠቀምኩ እንጂ አልተጎዳሁም ።እንደ ሽንፈት አልቆጥርም፤ቃሉ አሸነፈኝ፤ያስተማሩኝ ይባረኩ። ትልቁ ችግር ከስህተት አለመማር እና ልብን እልከኛ ማድረግ ነው፤ሞኝነት ነው።ለማወቅ የሚጥር ሰው፣በልቤ ሰፊነት "ቃሉ ግን ምን ይላል?" ፤ "...