አምልኮተ ሰብእ ከምንጩ ይነቀል! ለዘማሪ ልዑልሰገድ የቀረበ የኑፋቄ ምንጭ ምላሽ ።
አምልኮተ ሰብእ ከምንጩ ይነቀል! መግባት ይቻላል ! በዚህ ርዕስ ላይ ለመጻፍ ያነሳሳኝ የሰሞኑ ገጠመኝ ነው።ዘማሪው ነው።ቋንቋው ሰብዒ የሆነለት።ተስፋም እምነቱ እና ትምክቱም ሰብዒ የሆነለት።ከአትሮኖሱ ስሰበክ በመስማቱ ማከፈሉን ብነግረንም ።ከብዙ ተቋውሞ በኃላ ነው ።"መጀመሪያም ሳያምን ነውን!?" ፣ ምክንያቱም አራተ እየደጋገመ "ኢየሱስ ያድናል ማለት ክህደት /ምንfikiና / ነው" ብሏልና።የጥያቄ እና የተቋውሞ ናዳ ስወርድበት ፣ ከቤቷ ሰባክና ከአትሮኖሱ መስማቱን በመንገር "ከደሙ ንፁህ ነኝ" ለማለት አላፈረም ። ከጎበዛዝቱ የመጣውን ተግሳጽ እንደ ስድብም መቁጠሩ አስገርሞኛል።ከሁሉ በላይ የሚያስገርመኝ በቦታው የሰሙት እና በደብሩ የሞሉቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕዝቦች ፣ሳይጋጭባቸው 'ኢየሱስ ያድናል ማለት ክህደት ነው' ብለው መቀበላቸው ነው፤ከቦታው ተቋውሞ አልሰማንምና።"ቃለ ሕይወት ያሰማ" አዎን ያሰማ ወዳጄ፤ሄድክኮ።የአስተማረውም 'ሊቀ' ጥላቻ ካልሆነ በስተቀር ፣ በየትኛው መጽሐፍ ክፍል ስለትም ኢየሱስ የሚያድን እንደሆነ መመስከሩ ክህደት ሆኖ አያውቅም፤ጫፍ የወጣ ጥላቻ እና መመረዝ ካልሆነ በስተቀር።ከአንድ 'እውቅ' መምህር የማይጠበቅ ነው። ወንጌል የቋንቋ ማቀነባበሪያ አይደለም ሕይወት ነው።ወንጌል የቃላት ብልጫ ሳይሆን የቃሉ የነጠረ እውነት ነው። ዘማሪ ባወጣው በእምነት ቃል ፦"ኢየሱስ ያድናል ማለት ክህደት ነው " በሚለው በዚህች ቅጥበት ብቻ "ልክ ነው" ያለው ስንቱ ነው መሰላቹ ? ታዲያ የሚወዱቱ እና የሚያከብሩቱ ቀጥታ ከመምህር የሰሙት እንዴት ተበርዝው ይሁኑ !? ጌታ ይድረስላችሁ።በእኛ ሃገር ውሸት ስደጋገም እውነ...