ተአምረ ኢየሱስ የሚባለው መጽሐፍ ተአማኒነት አለው ?

 << ኢየሱስ ከ30 ዓመቱ በፊት ምልክት አድርጎ ነበርን? ተአምረ ኢየሱስ የሚባለው መጽሐፍ ተአማኒነት አለውን !? >>


👉" ተአምረ ኢየሱስ"የሚባለው መጽሐፍ ኢየሱስ ከፅንሰቱ እስከ ትንሳኤው ድረስ የሰራውን ተአምር የመዘገበ መጽሐፍ እንደሆነ ይነገራል፤ደግሞም ተምረናልም።

☝እንደ እግዚአብሔር ቃል <<ኢየሱስ ምልክት ማድረግን መቼ ጀመረ !? በእውነት ከ30 ዓመቱ በፊትም ምልክቶችን ያደርግ ነበርን !? >> የሚለውን ጥያቄ ይዘን ለመፈተሽ ተነስተናል ።

☝በእውነቱ.. ጌታ ከ30 ዓመቱ በፊት ምልክቶችን ያደርግ እንደነበረ የሚያሳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይኖር ይሁን !? 

☝በእርግጥም የሚጠቀሰው አይጠፋም ፤ያው ማንም ይጠቅሳልና ፥ ግን "ተአማኒነት አለው ወይ !?" የሚለው ጥያቄ ልነሳ ይገባል።


☝ለዚህ ማስረጃነት የሚጠቀሰው የመጽሐፍ ቅዱስ  ክፍል የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 20፥30 ነው።ቃሉ እንዲህ ይላል ፦ “ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤” 

☝ይህ ክፍል  'ኢየሱስ ክርስቶስ ከ30 ዓመቱ በፊት ምልክቶቹን አድርጓል' ስለመባሉ ማስረጃ ልሆን ይችላል ወይ !? የሚለውን እንፈትሽ በጥልቀት ፦

🌱 ኢየሱስ በዮሐንስ ወንጌል ያልተመዘገበ ሌላ ብዙ ምልክቶቹን እንዳደረገ ቃሉ ይገልጽልናል ።ግን ቃሉ የሚለው << ኢየሱስ ሌላ ብዙ ምልክቶችን፣በመጽሐፉ ያልተጻፉትን፣እንዳደረገ ነው፤ እንጂ ከ30 ዓመቱ  በፊት ምልክቶችን ስለማድረጉ አይነግረንም፤ይልቁንም ቃሉ የሚለው ፦ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገው ተአምር ሁሉ በቁጥር እንደ ብዛቱ መጠን እንዳልተጻፈ ነው። 

🌱ግን የኢየሱስ.. ምልክቶችን፣ ዮሐንስ ሁሉንም  አለመዘገቡ በራሱ ሌላ ሰው መመዝገቡን ያሳያልን !?

🌱ደግሞም ምልክቶቹ የተደረጉት ከ30 ዓመቱ በፊት በልጅነቱ ነው ለማለት ያስደፍራል !? አያስደፍርም።ምክንያቱም ዮሐንስ ስመሰክር <<ኢየሱስ ምልክቶቹን በደቀመዛሙርቱ ፊት አደረገ >>  እንጂ በልጅነቱም አደረገ አይልም።

🌱ኢየሱስ ምልክቶችን በደቀመዛሙርቱ ፊት ካደረገ ፣ ደቀመዛሙርቱ በ30 ዓመቱ፣ከውሃ ጥምቀት በኃላ መሰብሰቡ ደግሞ የመጽሐፉ እውነታ ነው፤ከዚህ ጋር ደግሞ ይቃረናል፤ትርክቱ።

🌱ስለዚህም ኢየሱስ ብዙ ምልክቶችን በደቀመዛሙርቱ ፊት፣ከ30 ዓመቱ ጀምሮ ምልክትን እንደሰራ እንረዳለን ።በዚህ እውነት መሠረት <<በልጅነቱ ምልክቶቹን አድርጓል>> ለማለት የሚጠቀሰው ይህ የዮሐንስ ወንገል ምዕራፍ 20፥30 አያስከድም እንላለን ።

☝ ሌላው ደግሞ ኢየሱስ ከ30 ዓመቱ በፊት ምልክት እንዳልሰራ የሚያስረዳው ክፍል የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 2፥11 ነው።ቃሉም እንዲህ የሚል ነው ፦ “ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።”ዮሐ 2፥11

☝በዚህ ክፍል መሠረት በገሊላ ቃና የተደረገው ምልክት ፦

🌱1ኛ.ዮሐንስ እንዳለው በደቀመዛሙርቱ ፊት የተደረገ ምልክት ነው ፣

🌱2ኛ.የመጀመሪያው ምልክትም ነው፣ 

🌱3ኛ."ክብሩን ገለጠ" እንደሚል ክብሩም የተገለጠበት የመጀመሪያው ምልክት ነው።

☝በዚህ ጊዜ ነው እንጂ ክብሩ የተገለጠው  ከ30 ዓመቱ በፊት እንዳልሆነ ግልጽ ነው ።


[ስለዚህም ምክንያት ኢየሱስ በልጅነቱ ምልክት አላደረገም ፤ 'ተአምረ ኢየሱስ' የሚባለው መጽሐፍ ተአማንነት የለውም እንላለን]


የምነቀለው ይነቀላል የምተከለው ይተከላል በኢየሱስ ስም !

#መልስ አለኝ የሚል ሁሉም ይምጣ።

Comments

Popular posts from this blog

"ደብተራ ማን ነው?" ጸረ ደብተራ ንቅናቄ በሊቀ ጠበብት በዶክተር ዘሪሁን ሙላቱ

ካህናት ነን

የኢየሱስን እናት ብፅዕት ማርያምን አትሳደቡ! (2)