Posts

ክርስቶስ ሁለት ልደት አለው !?

  ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ልደት አለውን !? #ኢየሱስ ክርስቶስን ተዋህዶች "ሁለት ልደት አለው ብለው" ያስተምራሉ ፤""ቅድመዓለም ከአብ ያለእናት ድኅረ ዓለም ከድንግል ካለአባት ከድንግል የተወለደው ነው። "" በማለት ። ቅብአት የሚባሉት ደግሞ ሦስት ልደት ነው ይላሉ ፣ በሁለት ልደት ዕሳቤ ላይ ፣   "  አብ ከድንግል ማርያም ማኅጸን በሥጋ ወለደው "  ይህንን ሃሳብ በመጨመር ያምናሉ ። የቅብአቶች አስተምህሮ በግልጽ ውድቅ የሆነ ስለሆነ ትኩረቴን በተዋህዶች አስተምህሮ ላይ አደርጋለሁ ።በተዋህዶች አስተምህሮ ላይ በስፋት የሚያትተው ሃይማኖት አበው መጽሐፍ ነው፤ከቀደምት አባቶች። ይህንን የሚያነብ ሰው ጸሐፊው አባቶችን በስህተትነት ለመፈረጅ ሳይሆን ሰው መሠረታዊ ነገር እንዳይረዳ ያደረገ አገላለጽ ስለሆነ ፣ለማስገንዘብ እና የምናምነው እምነት የተጠቀምነው ቃላት ስለማይገልጹ ልዩ ትርጉም ስለሚሰጡ እርማት ለመስጠት በማሰብ ብቻ ነው ።ሃይማኖት አበው ላይ ብፁዕ ዘሄሬነዎስ ስለኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ይለናል ፦ "" በሰው ባህሪይ ሰው የሆነ እርሱ ነው ፣ከአብ የተወለደ ፣ ከባህሪይ አምላክ የተገኘ የባህሪይ አምላክ ፣ የዘለዓለም ንጉሥ እርሱ ነው።.."" ከዚህ ክፍል የሚንረዳው ኢየሱስ ፦ ✍️ ሙሉእ ሰው እንደሆነ፣ ✍️ከአብ እንደተወለደ ና ✍️ ከአብ የተገኘ አምላክ እንደሆነ ነው። *ትኩረት የምናደርገው በኢየሱስ ከአብ መወለድ ላይ ነው።ስለዚህም ከአብ "እንዴት ተወለደ ? አምላክ ሆኖ ሳለ " ብባል መልሳቸው ፣ አብ በአፉ ቃል እንደወለደው ከመጽሐፉቱ እንረዳለን ፦ "ቃል ከአብ ያለ ድጋሚ ወጣ ፣ድንግልም ያለ ድካሚ ወለደችው "እን...

ቅዱሳን ንንን

              መግቢያ          ከአንዴ ወንዴም ጋር በመልካም መንፈስ በፊት ገጼ ፣በውስጥ መስመር "በጥያቄና መልስ ውይይት" መነጋገር ጀምርን ። ምንም እንኳን የግል ማንነት ወደ መተዋወቅ ባንሄድም መልካም ውይይት አድርገናል ።ልክ በአካል እንደሚንተዋወቅ ሰው። ብዙ ዓመት ጓደኛ እንደሆንን ሰዎች። ያለ ምንም ስድብ ፣ንቀት ፣ ሃሳብ አንሸራሽረናል።ይህ ዘመናዊነት ነው።ለዚህ ጥበባዊ ውይይት አለማመስገን አልችልም ። ለሁላችንም ምሳሌ የሚሆን ነው።ርዕሱ ላይ ብቻ ትኩረት መስጠት ፣ የምናምነው ነገርን በየዋህት መንፈስ ማቅረብ ፣የመቀበልና ያለ መቀበል መብት በማክበር ተወያይተናል ፣ይህ የዘመናዊነት ጥግ ነው። ስለ መልካም ምልልሳችን አመሰግናለሁ ።ክበርልኝ!  በውይይታችን የቀረበውን ሃሳብ በሁሉም ዘንድ ማንሸራሸር ስለፈለኩ ለሁሉም አጋርቼ ነበር።ቅዱሳን ሁለንም የማወቅ ጸጋ ፣ በሁለም ቦታ የመገኘት ጸጋ አላቸው የሚለውና ፣  ጸጋ የሞላብሽ ሆይ የሚለውን ቃል ትርጓሜ ፣ የውይይታችን ቁልፍ ነጥብ ነበር። በዚህም ላይ የብዙዎች እምነት ከእግዚአብሔር ቃል የወጣ እንደሆነ ተመለከትኩ ። ስለሆነም የተቻለኝን ሰፊ ማብራሪያ ለማቅረብ ወደድኩ።ስለሆነም ከታች በተዘረዘሩት ነጥቦችን ላይ ጹሐፍ የማቀርብ ይሆናል፦ 1.አምላክነት ምንድነው !? 2.የቅደሳን ሁለንም የማወቅ ጸጋ ! 3.የቅደሳን በሁለ ቦታ የመገኘት ጸጋ ! 4. "ጸጋ የሞላብሽ ሆይ " ማለት ምን ማለት ነው !? 4.የቅደሳን ጸሎትን የመስማት ጸጋ ! 5.ያረፉ ቅደሳን ስለእኛ ምህረትን ይምናሉ !? መልካም ምንባብ ይሁን ! ብዙ የሚታተርፉበት ይሁን ! 1.አምላክነት ምንድነው !? ስለ እግዚአብሔር አምላክነት ...

ካህናት ነን

 "ካህናት ነን "              ብዙ ግዜ እናስተምራለን እንጂ አንቀበለውም #በተለያየ_ትምህርቶች_ላይ_አስተያየት_ግሳጼ በተለይ ለታዋቂ 'አገልጋዮች' /ሰዎች/ ስቀርብ ቃሉን መቀበል አንወድም።  ይህንን ቃል "አማኝ ሁሉ አገልጋይ አይደለም" ለሚሉ ሰዎች ለመከራከያነት ከመጠቀም ውጪ እኛው ራሳችን ይህንን ቃል አንቀበለውም። አንድ አስተማሪ ስገሰጽ "አንተ የምን ቤት ነህ!?" ፣ "ቁጭ ብለ በሚሰራው ላይ መናገር ብቻ! ወሬኛ! " ፣ "እስኪ ምን ሰርተሃል!?" ፣ "እሱ ያስተምራል አንተ ማንን አስተምረ ታውቃለህ !?" የሚሉ ሃሳቦች ይነሳሉ ።እነዚህ ሃሳቦች ቃሉን በጥንቃቄ ካለማወቅ የመነጩም ናቸው ።ምክንያቱም ቃሉ የሚለው ፦ “የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ #በጥበብ_ሁሉ_እርስ_በርሳችሁ_አስተምሩና_ገሥጹ፤ ”(ቆላስይስ 3፥16) ፣ የሚል ነው። *የቃሉ እውነታ የሚያሳየው አማኞች ሁሉ አገልጋዮች ስለሆኑ ፣በጥበብ ሁሉ እርስ በእርስ እንደጸጋቸው የሚያስተምሩ ፥ የሚገስጹም ፥ እንደሆኑም የሚገልጽ ነው።ስለዚህም የአስተማሪነት ፀጋ ያለውን ወይም የመጋቢት ፀጋ ያለውን ለመገሰጽ የግድ የእሱ ዓይነት ፀጋ አያስፈልግም ።"እርስበእርስ" እንደሚል መጋቢውን - መካሪ ልገስጽ ይችላል ፣አስተማሪውን -እውቀትን የመግለጽ ጸጋ ያለው ልገስጽ ይችላል ደግሞም ሁሉንም መንፈስን መመርመር የሚችል ልመረምር ይችላል ። *ስለዚህም አንድን አስተማሪ ለመገሰጽ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅ ፐጅ ወይም ገጽ ወይንም የመድረክ አገልግሎት ሳይሆን የሚያስፈልገው "በክርስቶስ ካህን" መሆን ብቻ ነው የሚያስፈልገው ። ስለዚህም ተግሳጽ ለቀረበላቸው ሰዎች ...

ታቦትና ውዝግቡ!!

 [[ታቦቱና ውዝግቡ!]] ከዚህ በፊት "ነገረ ታቦት" ብዬ በጻፍኩት ላይ የአቅሜን ለመለገስ እንደተጣጣሪኩ ታውቃላችሁ ፣ይህ ጹሑፍ በዚህ ጹሑፍ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች የቀረበ መልስ ነው! [["ታቦትና መሰዊያ " የቃላት ጨዋታ!]] #በኢኦተቤክ | ድሮ ድሮ "ታቦታችን የሙሴ ታቦት ነው፣የቃል ኪዳኑ ታቦት ነው ፣  "እግዚአብሔር እንድንሰራ አዝዞን ነው የሠራነው " ይባል ነበር።ደግሞም "ለምን ይባዛል!?" ስባል እግዚአብሔር ሙሴ ከሰበረው በኃላ "እንደገና ሥራ ብሏል" በማለት ፥ ታዝዘን እንደበፊቱ ነው የሠራነው፤ያባዛነው የሚል መልስ ይሰጥ ነበር (ዓምደ ሃይማኖት app ይመልከቱ) ።አሁን አሁን ደግሞ ከኢኦተቤክ አንዳንድ ወንድሞች ታቦታችን የሙሴ ታቦት አይደለም ፥ ምክንያቱም የሙሴ ታቦት አራት ካህናት ይሸከማሉ ፥ የእኛ ታቦት የአድስ ኪዳን ታቦት ነው፤ሥጋውና ደሙ የሚቀርብበት እቃ ስለሆነ "ታቦት" ብለን እንጠራለን ፤"ጽላትም መሰዊያም" ተብሎ ይጠራል የሚል ነው።[ለውጥ ታይቷል በትንሹም ] *ወደ ርዕሰ ከመግባቴ በፊት አንድ ሁለት ነገር ልበላችሁ ፦ እኔ ወንድማችሁ ገና በጌታ በሆንኩበት ወራት ለውይይት ተጠራው ፣ አንድ ወንድም ስለ ታቦት ጥያቄ በማቅረቤ ፣ ይመልሳል ወደሚለው ወንድም ፣ የራሱ ደቀመዛሙርት ወደሰበሰበው ወሰደኝ።እኔም " እሺ" ብዬ ሄድኩ።ወደቤቱ ከደረስን በኃላ ከሰላምታ በኃላ ቁጭ አልን።ያመጣኝ ልጅ የመጣንበትን ርዕስ ጉዳይ አበሰረ።እኔ "የኢኦተቤክ ታቦት የሙሴ ታቦት አይደለም፤ ታቦት መባልም የለበትም" ብዬ ያቀረብኩትን ሃሳብ አቀረበለት ። ይመልሳል የተባለውም ልጁም እንደ ወሰደ "እመልሳለሁ፥አሳያ...

ራዕይ ጥናት ከም.4-22

  በዓለም ለሚከሰቱ ነገሮች ከበስተጀርባ ያለውን እውነታ ለማውቅ መጽሐፍ ቅዱስን እናጥና! እንወቀው! እንጽና !                    (ራዕይ ጥናት ከም.4-22) “ከዚያ በኋላም አየሁ፥ እነሆም በሰማይ የተከፈተ ደጅ፥ እንደ መለከትም ሆኖ ሲናገረኝ የሰማሁት ፊተኛው ድምፅ፦ ወደዚህ ውጣና ከዚህ በኋላ ሊሆን የሚያስፈልገውን ነገር አሳይሃለሁ አለ።”ራእይ 4፥1 ዮሐንስ ስለ 7ቱ አብያተክርስቲያናት በአስቸኳይ ልሆን የሚገባውን ከተመለከተ በኃላ ፣ በምዕራፍ 4 ደግሞ ሌላ ገና ልሆን የሚገባው ነገር ይመለከታል ። (ራዕይ መጽሐፍ ያለፈ ታርክ እየተረከልን አይደለም ) “ወዲያው በመንፈስ ነበርሁ፤ እነሆም፥ ዙፋን በሰማይ ቆሞአል በዙፋኑም ላይ ተቀማጭ ነበረ፤”ራእይ 4፥2 ዮሐንስ አብ በዙፋኑ ተቀምጦ እያለ ይመለከታል ፣ “በዙፋኑ ዙሪያም ሀያ አራት ዙፋኖች ነበሩ፥ በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው በራሳቸውም የወርቅ አክሊል ደፍተው ሀያ አራት ሽማግሌዎች ተቀምጠው ነበር።” ራእይ 4፥4 እነዚህ 24 ሽማግሌዎች የተባሉት በብሉይና በአድስ ክዳን ያሉቱ መላው የእግዚአብሔር ቤተሰብ ቁጥር ነው ፣ “ከዙፋኑም መብረቅና ድምፅ ነጐድጓድም ይወጣል፤ በዙፋኑም ፊት ሰባት የእሳት መብራቶች ይበሩ ነበር፥ እነርሱም ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው።”ራእይ 4፥5 ዮሐንስ ስመለከት ሰባት(በሙላት) የእግዚአብሔር መንፈስ አለበት በዙፋኑ ፊት፣ “በዙፋኑም ፊት ብርሌ የሚመስል የብርጭቆ ባሕር ነበረ። በዙፋኑም መካከል በዙፋኑም ዙሪያ፥ በፊትና በኋላ ዓይኖች የሞሉአቸው አራት እንስሶች ነበሩ።”ራእይ 4፥6 ዮሐንስ ስመለከት አራት እንስሶች (በዓለም በአራቱ አጥቃጫዎች ያሉት ፍጥረታት በሙሉ በፊቱ አሉ፣...